መቅደላ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማህበር 

መቅደላ ኮንስትራክሽን ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በኢትዮጵያ ንግድ ሕግ ቁጥር 686/2002 መሰረት ህጋዊ አውቅና አግኝቶ እ.ኤ.አ በ2008 የተቋቋመ በኮንስትራክሽን ስራ ዘርፍ የተሰማራ የጋፋት ኢንዶዉመንት የገቢ ማስገኛ ኩባንያ ነዉ፡፡ ኩባንያው በክልሉ እና በሀገር አቀፍ ደረጃ በሚካሄዱ፡-

  • የመንገድ
  • የድልድይ
  • የህንፃ ግንባታ ፕሮጀክቶች

እንዲሁም በማሽነሪ ኪራይ አገልግሎት ተሰማርቶ የሚገኝ ኩባንያ ነው፡፡

 

DSC_0115

Rethinking construction

ይህነ ለማሳካትም የሚከተሉትን እሴቶች የእለት ተእለት የስራ መመሪያው አድርጎ የሚንቀሳቀስ ኩባንያ ሲሆን እነዚህም፡-

  • ተልዕኳችንና ራዕያችንን ለማሣካት በቁርጠኝነት እንሰራለን !
  • በውጤት መለካትን እናምናለን !
  • በጊዜና በጥራት መፈፀም መለያችን ነው !
  • የኪራይ ሰብሳቢነት አስተሳሰብን አጥብቀን እንታገላለን !
  • ቁጠባን ባህላችን እንደርጋለን !
  • ለወጣቶችና ለሴቶች የስራ ዕድል መፍጠር የስራችን አንዱ አካል እናደርጋለን !
  • ታማኝነት፤ ሚዛናዊነትና ቅንነት ያለው አገልግሎት መስጠት መለያችን እናደርጋለን !
  • የአካባቢ ደህንነትን እንጠብቃለን !

የሚሉት ናቸው፡፡

Service, Quality & Value

ኩባንያው ታማኝነት፣ጥራትና ቅልጥፍናን መርሁ በማድረግ በድልድይ፣በመንገድና በህንጻ ግንባታ ዘርፍ የተሰማራ ሲሆን የኮንስትራክሽን ማሽነሪዎችና ተሽከርካሪዎችን የማከራየት አገልግሎትም ይሰጣል፡፡በዚህ መርህ በመመራትም መቅደላ ኮንስትራክሽን ከተቋቋመ ጀምሮ ባለፉት ስድስት አመታት 23 ኪ.ሜ የጠጠር መንገድን ጨምሮ ከ 40 የሚበልጡ የግንባታ ፕሮጀክቶችን አከናውኗል፡፡እነዚህም እያንዳንዳቸው የተቀመጠላቸውን የጥራት መስፈርት አሟልተው በመገንባታቸው ኩባንያው አንድም ለደንበኞቹ እርካታን መፍጠር ችሏል፤ሌላም ለራሱ ምስጋናና ተመራጭነትን አግኝቷል፡፡

በዚህም ለበርካቶች የስራ እድልን መፍጠር ችሏል፤ክልሉም በዘርፉ እያደረገ ያለውን ጥረት በማገዝ የዘርፉን ልማት በመደገፍ ላይ ይገኛል፡፡እነዚህም ተመራጭነታችንን ያጎሉታል፡፡

በመሆኑም በሚከተሉት የስራ ዘርፎች ማለትም፡-

  • መንገድ፣
  • ድልድይ እና
  • ህንጻ ግንባታ እንዲሁም
  • የኮንስትራክሽን ማሽነሪና ተሽከርካሪ ኪራይ ቢያስፈልግዎ

ምላሻችን ፈጣን ነው፡

 

DSC_2697

መቅደላ ኮንስትራክሽን

   ስ.ቁ:-+251-582-266146/45

ፋክስ:-+251-582-266146
                ድረ-ገጽ:- www.mekdellaconstruction.net   

አድራሻ:- ባህር ዳር፣ሹም አቦ ክፍለ ከተማ፣(ቀበሌ 08)